አማርኛ: Open Bible Stories

Updated ? hours ago # views See on DCS

6. እግዚአብሔር ለይስሐቅ ሚስት አዘጋጀለት

Image

አብርሃም በጣም ባረጀ ጊዜ ይስሐቅ ዕድሜው ለአቅመ አዳም ደረሰ። ስለዚህ አብርሃም ከአገልጋዮቹ አንዱን ወደ ዘመዶቹ ምድር ሄዶ ለልጁ ለይስሐቅ ሚስት እንዲያመጣለት ላከው።

Image

አገልጋዩም የአብርሃም ዘመዶች ወደሚኖሩበት ምድር ከረጅም ጒዞ በኋላ ደረሰ። እግዚአብሔርም የተላከውን የአብርሃምን አገልጋይ ወደ ርብቃ መራው። ርብቃ የአብርሃም ወንድም የልጅ ልጅ ነበረች።

Image

ርብቃ ቤተ ሰቦቿን ትታ ከአገልጋዩ ጋር ወደ ይስሐቅ ቤት ለመሄድ ተስማማች። እንደ ደረሰችም ይስሐቅ አገባት።

Image

ከረጅም ጊዜ በኋላ አብርሃም ሲሞት እግዚአብሔር ከአብርሃም ጋር የገባው የተስፋ ቃል ኪዳን ሁሉም ወደ ይስሐቅ ተላለፈ። እግዚአብሔር ለአብርሃም ማንም ሊቆጥር የማይችል ዘር እንደሚኖረው ተስፋ ሰጥቶት ነበር። ይሁን እንጂ የይስሐቅ ሚስት ርብቃ ልጅ ልትወልድ አልቻለችም።

Image

ይስሐቅ እግዚአብሔርን ለመነ፣ እግዚአብሔርም ርብቃ መንታ ልጆችን እንድታረግዝ ፈቀደ። ሁለቱ ልጆች በርብቃ ማኅፀን ሳሉ እርስ በርሳቸው ይታገሉ ነበር። ርብቃም በማኅፀንዋ እየሆነ ያለው ምን እንደሆነ እግዚአብሔርን ጠየቀች።

Image

እግዚአብሔርም ርብቃን አላት፣ ‹‹በማኅፀንሽ ካሉት ከሁለቱ ልጆችሽ ሁለት ሕዝቦች ይወጣሉ። እነርሱም እርስ በርሳቸው ይታገላሉ። ታላቁም ታናሹን ያገለግላል›› አላት።

Image

የርብቃ ልጆች በተወለዱ ጊዜ ታላቁ ልጅ ቀይና ፀጉራም ሆኖ ወጣ፤ ‹ኤሳው› ሲሉትም ስም አወጡለት፤ ታናሹም ልጅ የኤሳውን ተረከዝ ይዞ ወጣ፤ ስሙንም ‹ያዕቆብ› ሲሉ አወጡለት።

የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ፡- ከዘፍጥረት 24፡1-25፤ 26፡፡