አማርኛ: Open Bible Stories

Updated ? hours ago # views See on DCS

7. እግዚአብሔር ያዕቆብን ባረከ

Image

ልጆቹም እያደጉ ሲሄዱ ያዕቆብ በቤት መቆየትን ይወድ ነበር። ኤሳው ግን አደን ማደን ይወድ ነበር። ርብቃ ያዕቆብን ትወድደው ነበር፣ ይስሐቅ ግን ኤሳውን ይወድደው ነበር።

Image

ከዕለታት አንድ ቀን ኤሳው ከአደን ተመልሶ ሲመጣ በጣም ተርቦ ነበር። ኤሳው ያዕቆብን ‹‹እባክህ ካዘጋጀኸው ምግብ ትንሽ ስጠኝ›› አለው። ያዕቆብም “በመጀመሪያ የብኩርናህን መብት ስጠኝ” ሲል መለሰለት። ስለዚህም ኤሳው የብኩርናውን መብት ለያዕቆብ ሰጠው። ከዚያም ያዕቆብ ከሠራው ምግብ ሰጠው።

Image

ይስሐቅ ኤሳውን ሊባርከው ፈለገ። ነገር ግን ይህን ከማድረጉ በፊት ርብቃና ያዕቆብ ይስሐቅን አታለሉት። ያዕቆብ ኤሳውን መስሎ ወደ ይስሐቅ ቀረበ።በዚያ ጊዜ ይስሐቅ አርጅቶ ነበር፤ ማየትም አይችልም ነበር። ስለዚህም ያዕቆብ የኤሳውን ልብሶች ለብሶ የፍየል ለምድ በአንገቱና በእጆቹ አድርጎ ወደ ይስሐቅ በመቅረብ ይስሐቅን አታለለው።

Image

ያዕቆብ ወደ ይስሐቅ መጣና እንዲህ አለው፣ ‹‹እኔ ኤሳው ነኝ፤ መጥቻለውና ባርከኝ››አለው። ይስሐቅ የፍየሉን ፀጉር ዳሰሰና የልብሱንም ጠረን አሽትቶ ኤሳው እንደ ሆነ አሰበና ባረከው።

Image

ያዕቆብ የብኵርና መብቱንና በረከቱን አታልሎ ስለ ወሰደበት ኤሳው ያዕቆብን ጠላው። አባታቸው ሲሞት ሊገድለውም አቀደ።

Image

ነገር ግን ርብቃ የኤሳውን እቅድ ሰማች። ስለዚህም እሷና ይስሐቅ ከዘመዶቹ ጋር እንዲኖር ወደ ሩቅ አገር ያዕቆብን ሰደዱት።

Image

ያዕቆብ ለረዥም ዓመታት ከርብቃ ዘመዶች ጋር ኖረ። በዚያም ጊዜ ትዳር መስርቶ 12 ወንዶች ልጆችና 1 ሴት ልጅ ወለደ። እግዚአብሔርም በጣም አበለጸገው።

Image

በከነዓን ከኖረበት ከሃያ (20) ዓመታት በኋላ ያዕቆብ ከቤተ ሰቡ፣ ከአገልጋዮቹና ከመንጋው ሁሉ ጋር ወደ ከነዓን ምድር ተመለሰ።

Image

ኤሳው አሁንም ሊገድለኝ ያስብ ይሆናል ብሎ በልቡ ስላሰበ ያዕቆብ እጅግ በጣም ፈራ። ስለዚህም የእጅ መንሻ እንዲሆነው የብዙ ከብቶች መንጋ ስጦታ አድርጎ ለኤሳው ላከለት። ከብቶቹን ያመጡለት የያዕቆብ አገልጋዮች ኤሳውን ‹‹አገልጋይህ ያዕቆብ እነዚህን ከብቶች ልኮልሃል። እርሱም በቅርቡ ይመጣል›› አሉት።

Image

ኤሳው ግን ቀድሞውኑ ያዕቆብን ይቅር ብሎት ስለ ነበር ዳግም ለመገናኘት በመብቃታቸው ደስ አለው። ያዕቆብ በከነዓን ምድር በሰላም ኖረ፤ ከዚያም ይስሐቅ ሞተ። ያዕቆብና ኤሳውም ቀበሩት። እግዚአብሔር ለአብርሃም የገባለት የቃል ኪዳኑ ተስፋ አሁን ከይስሐቅ ወደ ያዕቆብ ተላለፈ።

የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ፡- ከዘፍጥረት 25፡27-33፡20፡፡