አማርኛ: Open Bible Stories

Updated ? hours ago # views See on DCS

10. ዐሥሩ መቅሠፍቶች

Image

ሙሴና አሮን ወደ ፈርዖን ሄደው “የእስራኤል አምላክ “ሕዝቤን ልቀቅ! ይልሃል” አሉት። ፈርዖን ግን አልሰማቸውም። እስራኤላውያን ነጻ ሆነው እንዲሄዱ በመልቀቅ ፈንታ ከበፊቱ የከበደ ሥራ እንዲሠሩ አስገደዳቸው!

Image

ፈርዖን ሕዝቡን አልለቅም ማለቱን ቀጠለ፤ ስለዚህ እግዚአብሔር በግብፅ ላይ ዐሥር መቅሠፍቶችን ላከ። እግዚአብሔር በእነዚህ መቅሠፍቶች አማካይነት ከፈርዖንና ከግብፅ አማልክት ሁሉ ይልቅ ኃያል መሆኑን ለፈርዖን ዐሳየው።

Image

እግዚአብሔር የዓባይን ውሃ ወደ ደም ለወጠው፣ ነገር ግን ፈርዖን አሁንም እስራኤላውያንን እንዲሄዱ አልለቀቃቸውም።

Image

እግዚአብሔር በግብፅ ሁሉ ላይ እንቁራሪቶችን ላከ። ፈርዖን እንቁራሪቶቹን እንዲያርቅ ሙሴን ለመነው። እንቁራሪቶቹ ሁሉ ከሞቱ በኋላ ግን ፈርዖን ልቡን እንደገና አደነደነና እስራኤላውያንን ከግብፅ እንዲወጡ አልለቀቃቸውም።

Image

ስለዚህ እግዚአብሔር የቅማል መቅሰፍት ላከ። ከዚያም የዝንብ መቅሰፍት ላከ። ፈርዖን ሙሴንና አሮንን ጠራና መቅሠፍቱን ካቆሙ እስራኤላውያን ከግብፅ መሄድ እንደሚችሉ ነገራቸው። ሙሴ በጸለየ ጊዜ እግዚአብሔር የዝንብ መቅሰፍቶችን ሁሉ ከግብፅ አስወገደ። ነገር ግን ፈርዖን ልቡን አደነደነና ሕዝቡን ነፃ እንዲወጡ አልለቀቃቸውም።

Image

ቀጥሎ እግዚአብሔር የግብፃውያን ከብቶች ሁሉ ታመው እንዲሞቱ አደረገ። ነገር ግን የፈርዖን ልብ ስለደነደነ እስራኤላውያንን አልለቀቀም።

Image

ከዚያም እግዚአብሔር በፈርዖን ፊት ዐመድ ወደ ሰማይ እንዲበትን ለሙሴ ነገረው። ዐመዱን በበተነ ጊዜ በግብፃውያን ላይ የሚያም ቊስል ሆነባቸው፣ በእስራኤላውያን ላይ ግን ቊስሉ አልሆነባቸውም። እግዚአብሔር የፈርዖንን ልብ ስላደነደነ ፈርዖን እስራኤላውያንን አልለቀቀም።

Image

ከዚያ በኋላ እግዚአብሔር በግብፅ ያለውን አብዛኛውን ቡቃያ ያሚያጠፋና ከቤት ውጪ የነበረውን ማንኛውንም ሰው የሚገድል በረዶ ላከ። ፈርዖን ሙሴንና አሮንን ጠርቶ፣ ‹‹በድዬአለሁ። መሄድ ትችላላችሁ›› ብሎ ነገራቸው። ስለዚህ ሙሴ ጸለየ፣ በረዶውም ከሰማይ መዝነቡን አቆመ።

Image

ነገር ግን ፈርዖን እንደ ገና ኃጢአት ሠራ፤ ልቡንም አደነደነ። እስራኤላውያንን አልለቀቀም።

Image

ስለዚህ እግዚአብሔር በግብፅ ላይ የአንበጣዎችን መንጋ አመጣ። እነዚህ አንበጣዎች ከበረዶው የተረፈውን ሰብል ሁሉ አወደሙት።

Image

ከዚያም እግዚአብሔር ለሦስት ቀን የቆየ ጨለማ ላከ። ጭለማው በጣም ከባድ ስለነበር ግብፃውያን ከቤታቸው ሊወጡ አቻሉም ነበር። እስራኤላውያን በሚኖሩበት ስፍራ ግን ብርሃን ነበረ።

Image

ከእነዚህ ዘጠኝ መቅሠፍቶች በኋላ እንኳ ፈርዖን አሁንም እስራኤላውያንን አልለቅም አለ። ፈርዖን መስማት እንቢ ስላለ፣ እግዚአብሔር አንድ የመጨረሻ መቅሠፍት ለመላከ ወሰነ። ይህ መቅሰፍት ፈርዖን ዐሳቡን እንዲቀይር ያደርጋል።

የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ፡- ከዘጸአት 5-10፡፡