አማርኛ: Open Bible Stories

Updated ? hours ago # views See on DCS

25. ሰይጣን ኢየሱስን ፈተነው

Image

ኢየሱስ ከተጠመቀ በኋላ ወዲያውኑ፣ መንፈስ ቅዱስ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው፣ እዚያም አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾመ፡፡ ከዚያም ሰይጣን ወደ ኢየሱስ መጣና ኃጢአት እንዲሠራ ኢየሱስን ፈተነው፡፡

Image

‹‹የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንክ፣እነዚህን ድንጋዮች ወደ እንጀራ ለውጥ›› በማለት ሰይጣን ኢየሱስን ፈተነው፡፡

Image

ኢየሱስ፣ ‹‹‹ሰዎች ለመኖር እንጀራ ብቻ አያስፈልጋቸውም፣ ነገር ግን እግዚአብሔር የሚናገረው እያንዳንዱ ቃል ያስፈልጋቸዋል› ተብሎ በእግዚአብሔር ቃል ተጽፎአል!›› ብሎ መለሰለት፡፡

Image

ከዚያም ሰይጣን ኢየሱስን ወደ ቤተ መቅደስ ጫፍ ወሰደውና፣ ‹‹የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክ ራስህን ወደ ታች ወርውር፣ ምክንያቱም፣ ‹ድንጋይ እግርህን እንዳይመታህ ይሸከሙህ ዘንድ እግዚአብሔር መላእክቱን ያዛል ተብሎ ተጽፎል››› አለ፡፡

Image

ነገር ግን ኢየሱስ ከእግዚአብሔር ቃል በመጥቀስ ለሰይጣን መለሰለት፡፡ ‹‹በእግዚአብሔር ቃል፣ ‹ጌታ አምላክህን አትፈታተነው› ተብሎ ተጽፎአል›› አለው፡፡

Image

ከዚያም ሰይጣን የዓለምን መንግሥታትና ክብራቸውን ሁሉ ዐሳየውና፣ ‹‹ወድቀህ ብትሰግድልኝ ይህን ሁሉ እሰጥሃለሁ›› አለ፡፡

Image

ኢየሱስ፣ ‹‹ከኔ ራቅ፣ አንተ ሰይጣን! በእግዚአብሔር ቃል፣ ‹ለጌታህ ለአምላክህ ስገድ እርሱንም ብቻ አምልክ› ተብሎ ተጽፎአል›› አለው፡፡

Image

ኢየሱስ ለሰይጣን ፈተና አልተሸነፈም፣ ስለዚህ ሰይጣን ለጊዜው ትቶት ሄደ፡፡ ከዚያ በኋላ መላእክት መጥተው ኢየሱስን አገለገሉት፡፡

የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ፡- ከማቴዎስ 4፡1-11፤ ማርቆስ 1፡12-13፤ ሉቃስ 4፡1-13፡፡