አማርኛ: Open Bible Stories

Updated ? hours ago # views See on DCS

36. የኢየሱስ መልክ ተለወጠ

Image

አንድ ቀን ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ሦስቱን፦ ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዮሐንስን ይዞ ብቻቸውን ሊጸልዩ ወደ ረጅም ተራራ ወጡ፡፡(ዮሐንስ የተባለው ደቀ መዝሙር ኢየሱስን ያጠመቀው ዮሐንስ አይደለም፡፡)

Image

ኢየሱስ በመጸለይ ላይ እያለ፣ ፊቱ እንደ ፀሐይ አበራ፣ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ፣ ንጻቱም በምድር ላይ ያለ ማንኛውም ሰው ሊያነጻው እስከማይችል ድረስ በጣም ነጭ ነበር፡፡

Image

በዚያን ጊዜ ሙሴና ነቢዩ ኤልያስ ታዩ፡፡ እነዚህ ሰዎች በመቶዎች ከሚቈጠሩ ዓመታት በፊት በምድር ላይ ይኖሩ ነበር፡፡ እነርሱም በቅርቡ በኢየሩሳሌም ስለሚሆነው ስለ ኢየሱስ ሞት ከእርሱ ጋር ተነጋገሩ፡፡

Image

ሙሴና ኤልያስ ከኢየሱስ ጋር በመነጋገር ላይ እያሉ ጴጥሮስ ኢየሱስን፣ ‹‹በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው፡፡ ሦስት ዳሶችን አንድ ለአንተ፣ አንድ ለሙሴ፣ እንዲሁም አንድ ለኤልያስ እንሥራ›› አለው፡፡ ጴጥሮስ የሚናገረውን አያውቅም ነበር፡፡

Image

ጴጥሮስ እየተናገረ እያለ፣ ብሩህ ደመና መጥቶ ከበባቸውና ከደመናውም ድምፅ፣ ‹‹በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፣ እርሱን ስሙት›› አለ፡፡ ሦስቱ ደቀ መዛሙርት ፈሩና መሬት ላይ ወደቁ፡፡

Image

በዚያን ጊዜ ኢየሱስ ዳሰሳቸውና፣ ‹‹አትፍሩ፣ ተነሡ›› አላቸው፡፡ ዙሪያቸውን ሲያዩ ከእነርሱ ጋር ያለው ኢየሱስ ብቻ ነበር፡፡

Image

ኢየሱስና ሦስቱ ደቀ መዛሙርት ከተራራው ወረዱ፡፡ በዚያን ጊዜ ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፣ ‹‹በዚህ ስለ ሆነው ነገር አሁን ለማንም አትናገሩ፡፡ እኔ በቅርብ ጊዜ እሞታለሁ፣ ተመልሼም ሕያውም እሆናለሁ፡፡ ከዚያ በኋላ ለሰዎች መናገር ትችላላችሁ፡፡››

የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ፡- ከማቴዎስ 17፡1-9፤ ማርቆስ 9፡2-8፤ ሉቃስ 9፡28-36፡፡