አማርኛ: Open Bible Stories

Updated ? hours ago # views See on DCS

11. ፋሲካ

Image

ፈርዖን እስራኤላውያንን ካልለቀቀ የግብፃውያን ሰዎችና የእንስሳቶቻቸውን መጀመሪያ የተወለዱትን ወንዶች ሁሉ እንደሚገድል እግዚአብሔር ፈርዖንን አስጠነቀቀው። ፈርዖን ይህን ቢሰማም እንኳ፣ አሁንም ማመንና ለእግዚአብሔር መታዘዝ እምቢ አለ።

Image

እግዚአብሔር በእርሱ ያመነ የማንኛውንም ሰው የመጀመሪያ ወንድ ልጅን ለማዳን መንገድ አዘጋጀ። እያንዳንዱ ቤተ ሰብ ፍጹም የሆነ የበግ ጠቦት መርጦ እንዲያርድ አዘዘ።

Image

እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን የጠቦቱን ደም በቤታቸው በር ላይ እንዲቀቡት፣ ሥጋውንም ጠብሰው ያለ እርሾ ከተጋገረው ቂጣ ጋር በፍጥነት እንዲበሉት ነገራቸው። ደግሞ በበሉት ጊዜ ከግብፅ ለመውጣት እንዲዘጋጁ ነገራቸው።

Image

እስራኤላውያን ልክ እግዚአብሔር እንዲያደርጉ እንዳዘዛቸው ሁሉንም ነገር አደረጉ። እኩለ ሌሊት ላይ እግዚአብሔር በመላው ግብፅ አልፎ መጀመሪያ የተወለደውን ወንድ ሁሉ ገደለ።

Image

የእስራኤላውያን ቤቶች ሁሉ በሮቻቸው ደም ተቀብተው ነበር፣ ስለዚህ እግዚአብሔር በቤቶቹ አለፈ። በቤቶቹ ውስጥ የነበረው ሁሉ ከሞት ተረፈ። እስራኤላውያን በጠቦቱ ደም ምክንያት ዳኑ።

Image

ግብፃውያን ግን በእግዚአብሔር አላመኑም፣ ትእዛዛቱንም አልፈጸሙም። ስለዚህ እግዚአብሔር በቤቶቻቸው አላለፈም። እግዚአብሔር የግብፃውያንን በመጀመሪያ የተወለዱ ወንዶችን በሙሉ ገደለ።

Image

በእስር ቤት ካለው በኵር ልጅ ጀምሮ እስከ ፈርዖን በኩር ልጅ ድረስ የግብፃዊያን የመጀመሪያ ወንድ ልጅ በሙሉ ሞተ። ከጥልቅ ሐዘናቸው የተነሣ በግብፅ የነበሩ ሰዎች ሁሉ ያለቅሱና ይጮኹ ነበር።

Image

በዚያው ሌሊት ፈርዖን ሙሴንና አሮንን ጠርቶ፣ “እስራኤላውያንን ይዛችሁ አሁኑኑ ከግብፅ ውጡ” አላቸው። ግብፃውያንም እስራኤላውያን በፍጥነት ከግብፅ እንዲወጡ አስቸኰሉአቸው።

የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ፡- ከዘጸአት 11፡1-12፡32፡፡