9. እግዚአብሔር ሙሴን ጠራው

ዮሴፍ ከሞተ በኋላ ዘመዶቹ በሙሉ በግብፅ ኖሩ። እነርሱና ዘሮቻቸው ለብዙ ዓመታት እዚያ መኖራቸውን ቀጠሉ፤ ብዙ ልጆችንም አፈሩ፤ እስራኤላውያንም ተብለው ተጠሩ።

ከመቶዎች ዓመታት በኋላ የእስራኤላውያን ቊጥር እየበዛ መጣ። ግብፃውያንም ዮሴፍንና እነርሱን ለመርዳት ዮሴፍ ያደረገውን ሁሉ ረሱ። እስራኤላውያን እየበዙ በመምጣታቸው ግብፃውያን ፈሯቸው። ስለዚህ በዚያን ጊዜ ግብፅን ያስተዳድር የነበረው ፈርዖን እስራኤሎችን ለግብፃውያን ባሪያዎች እንዲሆኑ አደረጋቸው።

ግብፃውያን እስራኤላውያንን የግንብ ሥራ እንዲሠሩና፣ ከተማዎችን ሁሉ እንዲገነቡ በኃይል ያስገድዷቸው ነበር። ከባዱ ሥራም ሕይወታቸውን አስቸጋሪ አደረገው። እግዚአብሔር ግን ባረካቸው፤ ብዙ ልጆችም ነበሯቸው።

ፈርዖን እስራኤላውያን ብዙ ሕፃናት እንዳሏቸው አየ፤ ስለዚህ ፈርዖን ከእስራኤላውያን ወንዶች ልጆች ሲወለዱ አባይ ወንዝ ውስጥ በመወርወር እንዲገድሉ ሕዝቡን አዘዘ።

በዚያን ጊዜ አንዲት እስራኤላዊት ሴት ወንድ ልጅ ወለደች። እርሷና ባለቤቷ የቻሉትን ያህል ልጁን ለመደበቅ ሞከሩ።

የልጁ ወላጆች ልጁን ከዚያ በላይ ሊደብቁት እንደማይችሉ በተረዱ ጊዜ ልጁ እንዳይሞት በሚንሳፈፍ ቅርጫት ውስጥ አድርገው በአባይ ወንዝ ዳር ባለው ቄጤማ ውስጥ ወንዙ ላይ እንዲንሳፈፍ ለቀቁት። ታላቅ እህቱም በልጁ ላይ የሚደርስበትን ለማየት በቅርብ ትከታተለው ነበር።

የፈርዖን ሴት ልጅ ቅርጫቱን አየችና በውስጡ ያለውን ተመለከተች። ሕፃኑን ባየች ጊዜ እንደ ልጇ አድርጋ ወሰደችው። እርሷም ልጁን ጡት የምታጠባ እስራኤላዊት ሴት ቀጠረች። የቀጠረቻትም ሴትዮ የልጁ እናት መሆኗን አላወቀችም ነበር። ልጁም አድጎ የናቱን ጡት መጥባት ባቆመ ጊዜ ሴትዮዋ ወደ ፈርዖን ልጅ መለሰችው። የፈርዖ ልጅም ስሙን ‹‹ሙሴ›› ብላው ጠራች።

ሙሴም ባደገ ጊዜ አንድ ቀን አንድ ግብፃዊ እስራኤላዊ የሆነውን ባሪያ ሲመታው አየ። ሙሴም እስራኤላዊ ወገኑን ሊያድነው ፈለገ።

ሙሴ ማንም ሰው ያላየ መስሎት ግብፃዊውን ገድሎ ቀበረው። ነገር ግን ሙሴ ያደረገውን አንድ ሰው አይቶት ነበር።

ሙሴ ያደረገውን ፈርዖን በሰማ ጊዜ ሊገድለው ፈለገ። ሙሴ ግን ከፈርዖን ወታደሮች ነፍሱን ለማዳን ወደ ምድረ በዳ ሸሸ።

ሙሴ ከግብፅ ምድር ርቆ ወደሚገኝ ምድረ በዳ በመሄድ የበጐች እረኛ ሆነ። ከዚያም አገር ሚስት አግብቶ ሁለት ወንዶች ልጆችን ወለደ።

አንድ ቀን ሙሴ በጐቹን እየጠበቀ ሳለ እሳት የሚነድበት ቊጥቋጦ ተመለከተ፤ ይሁን እንጂ ቊጥቋጦው አይቃጠልም ነበር። ሙሴም በደንብ ለማየት ወደ ቊጥቋጦው ጠጋ አለ። ወደሚቃጠለው ቊጥቋጦ ጠጋ ሲል የእግዚአብሔር ድምፅ ‹‹ሙሴ፤ በቅዱስ ስፍራ ቆመሃልና ከእግርህ ጫማህን አውልቅ›› አለው።

እግዚአብሔርም ‹‹የሕዝቤን ሥቃይ አይቻለሁና እስራኤልንም ከግብፅ ባርነት ነጻ እንድታወጣቸው ወደ ፈርዖን እልክሃለው። ለአብርሃም፣ለይስሐቅና ለያዕቆብ ተስፋ የሰጠኋቸውን የከነዓንን ምድር እሰጣቸዋለሁ አለ።››

ሙሴም ሕዝቡ ‹‹ማን ላከህ›› ብለው ቢጠይቁኝ ምን እላቸዋለሁ ሲል እግዚአብሔርን ጠየቀ። እግዚአብሔርም ሙሴን “እኔ ያለሁና የሚኖር ንኝ፤ ስለዝህ ‹ያለና የሚኖር ልኮኛል› ብለህ ንገራቸው›› አለው። ደግሞሜ ‹‹እኔ የአብርሃም፣ የይስሐቅና የያዕቆብ አምላክ ያህዌህ ነኝ። ስሜም ለዘላለም ይህ ነው” አለው።

ሙሴ ስለ ፈራ ወደ ፈርዖን መሄድ አልፈለገም። ምክንያቱም የንግግር ችሎታ የለኝም ብሎ በማሰቡ ነበር። ስለዚህም እግዚአብሔር የሙሴን ወንድም አሮንን አብሮት እንዲሄድና ሙሴን እንዲረዳው ላከው። እግዚአብሔርም ፈርዖን ሕዝቡን አለቅም በሚል ልቡን ሊያደነድን እንደሚችል ሙሴንና አሮንን አስጠነ ቃቸው።
የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ፡- ከዘጸአት 1-4፡፡