አማርኛ: Open Bible Stories

Updated ? hours ago # views See on DCS

9. እግዚአብሔር ሙሴን ጠራው

Image

ዮሴፍ ከሞተ በኋላ ዘመዶቹ በሙሉ በግብፅ ኖሩ። እነርሱና ዘሮቻቸው ለብዙ ዓመታት እዚያ መኖራቸውን ቀጠሉ፤ ብዙ ልጆችንም አፈሩ፤ እስራኤላውያንም ተብለው ተጠሩ።

Image

ከመቶዎች ዓመታት በኋላ የእስራኤላውያን ቊጥር እየበዛ መጣ። ግብፃውያንም ዮሴፍንና እነርሱን ለመርዳት ዮሴፍ ያደረገውን ሁሉ ረሱ። እስራኤላውያን እየበዙ በመምጣታቸው ግብፃውያን ፈሯቸው። ስለዚህ በዚያን ጊዜ ግብፅን ያስተዳድር የነበረው ፈርዖን እስራኤሎችን ለግብፃውያን ባሪያዎች እንዲሆኑ አደረጋቸው።

Image

ግብፃውያን እስራኤላውያንን የግንብ ሥራ እንዲሠሩና፣ ከተማዎችን ሁሉ እንዲገነቡ በኃይል ያስገድዷቸው ነበር። ከባዱ ሥራም ሕይወታቸውን አስቸጋሪ አደረገው። እግዚአብሔር ግን ባረካቸው፤ ብዙ ልጆችም ነበሯቸው።

Image

ፈርዖን እስራኤላውያን ብዙ ሕፃናት እንዳሏቸው አየ፤ ስለዚህ ፈርዖን ከእስራኤላውያን ወንዶች ልጆች ሲወለዱ አባይ ወንዝ ውስጥ በመወርወር እንዲገድሉ ሕዝቡን አዘዘ።

Image

በዚያን ጊዜ አንዲት እስራኤላዊት ሴት ወንድ ልጅ ወለደች። እርሷና ባለቤቷ የቻሉትን ያህል ልጁን ለመደበቅ ሞከሩ።

Image

የልጁ ወላጆች ልጁን ከዚያ በላይ ሊደብቁት እንደማይችሉ በተረዱ ጊዜ ልጁ እንዳይሞት በሚንሳፈፍ ቅርጫት ውስጥ አድርገው በአባይ ወንዝ ዳር ባለው ቄጤማ ውስጥ ወንዙ ላይ እንዲንሳፈፍ ለቀቁት። ታላቅ እህቱም በልጁ ላይ የሚደርስበትን ለማየት በቅርብ ትከታተለው ነበር።

Image

የፈርዖን ሴት ልጅ ቅርጫቱን አየችና በውስጡ ያለውን ተመለከተች። ሕፃኑን ባየች ጊዜ እንደ ልጇ አድርጋ ወሰደችው። እርሷም ልጁን ጡት የምታጠባ እስራኤላዊት ሴት ቀጠረች። የቀጠረቻትም ሴትዮ የልጁ እናት መሆኗን አላወቀችም ነበር። ልጁም አድጎ የናቱን ጡት መጥባት ባቆመ ጊዜ ሴትዮዋ ወደ ፈርዖን ልጅ መለሰችው። የፈርዖ ልጅም ስሙን ‹‹ሙሴ›› ብላው ጠራች።

Image

ሙሴም ባደገ ጊዜ አንድ ቀን አንድ ግብፃዊ እስራኤላዊ የሆነውን ባሪያ ሲመታው አየ። ሙሴም እስራኤላዊ ወገኑን ሊያድነው ፈለገ።

Image

ሙሴ ማንም ሰው ያላየ መስሎት ግብፃዊውን ገድሎ ቀበረው። ነገር ግን ሙሴ ያደረገውን አንድ ሰው አይቶት ነበር።

Image

ሙሴ ያደረገውን ፈርዖን በሰማ ጊዜ ሊገድለው ፈለገ። ሙሴ ግን ከፈርዖን ወታደሮች ነፍሱን ለማዳን ወደ ምድረ በዳ ሸሸ።

Image

ሙሴ ከግብፅ ምድር ርቆ ወደሚገኝ ምድረ በዳ በመሄድ የበጐች እረኛ ሆነ። ከዚያም አገር ሚስት አግብቶ ሁለት ወንዶች ልጆችን ወለደ።

Image

አንድ ቀን ሙሴ በጐቹን እየጠበቀ ሳለ እሳት የሚነድበት ቊጥቋጦ ተመለከተ፤ ይሁን እንጂ ቊጥቋጦው አይቃጠልም ነበር። ሙሴም በደንብ ለማየት ወደ ቊጥቋጦው ጠጋ አለ። ወደሚቃጠለው ቊጥቋጦ ጠጋ ሲል የእግዚአብሔር ድምፅ ‹‹ሙሴ፤ በቅዱስ ስፍራ ቆመሃልና ከእግርህ ጫማህን አውልቅ›› አለው።

Image

እግዚአብሔርም ‹‹የሕዝቤን ሥቃይ አይቻለሁና እስራኤልንም ከግብፅ ባርነት ነጻ እንድታወጣቸው ወደ ፈርዖን እልክሃለው። ለአብርሃም፣ለይስሐቅና ለያዕቆብ ተስፋ የሰጠኋቸውን የከነዓንን ምድር እሰጣቸዋለሁ አለ።››

Image

ሙሴም ሕዝቡ ‹‹ማን ላከህ›› ብለው ቢጠይቁኝ ምን እላቸዋለሁ ሲል እግዚአብሔርን ጠየቀ። እግዚአብሔርም ሙሴን “እኔ ያለሁና የሚኖር ንኝ፤ ስለዝህ ‹ያለና የሚኖር ልኮኛል› ብለህ ንገራቸው›› አለው። ደግሞሜ ‹‹እኔ የአብርሃም፣ የይስሐቅና የያዕቆብ አምላክ ያህዌህ ነኝ። ስሜም ለዘላለም ይህ ነው” አለው።

Image

ሙሴ ስለ ፈራ ወደ ፈርዖን መሄድ አልፈለገም። ምክንያቱም የንግግር ችሎታ የለኝም ብሎ በማሰቡ ነበር። ስለዚህም እግዚአብሔር የሙሴን ወንድም አሮንን አብሮት እንዲሄድና ሙሴን እንዲረዳው ላከው። እግዚአብሔርም ፈርዖን ሕዝቡን አለቅም በሚል ልቡን ሊያደነድን እንደሚችል ሙሴንና አሮንን አስጠነ ቃቸው።

የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ፡- ከዘጸአት 1-4፡፡