አማርኛ: Open Bible Stories

Updated ? hours ago # views See on DCS

13. እግዚአብሔር ከእስራኤል ጋር ያደረገው ቃል ኪዳን

Image

እግዚአብሔር እስራኤላውያንን በቀይ ባሕር ውስጥ ካሳለፋቸው በኋላ በምድረ በዳ ውስጥ ሲና ተብሎ ወደሚጠራ ተራራ ወሰዳቸው። ይህም ሙሴ የሚቃጠለውን ቊጥቋጦ ያየበት ተራራ ነው። ሕዝቡ በተራራው ሥር ድንኳኖቻቸውን ተከሉ።

Image

እግዚአብሔርም፣ ‹‹ለእኔ ብትታዘዙና ቃል ኪዳኔን ብትጠብቁ፣ የከበረ ርስት፣ የካህናት መንግስት፣ እንዲሁም ቅዱስ ሕዝብ ትሆኑኛላችሁ›› ብሎ ለሙሴና ለእስራኤል ሕዝብ ተናገረ።

Image

ሕዝቡ በመንፈሳዊነት ራሳቸውን ካዘጋጁ ከሦስት ቀን በኋላ፣ እግዚአብሔር በነጐድጓድ፣ በመብረቅ፣ በጢስ እንዲሁም ከፍ ባለ የመለከት ድምፅ በሲና ተራራ ላይ ወረደ። ወደ ተራራው እንዲወጣ የተፈቀደለት ሙሴ ብቻ ነበር።

Image

ከዚያም እግዚአብሔር ቃል ኪዳን ገባላቸውና እንዲህ አለ፣ ‹‹እኔ ከግብፅ ባርነት ያዳንኳችሁ፣ አምላካችሁ፣ ያህዌ ነኝ። ሌሎችን አማልክት አታምልኩ።››

Image

‹‹ጣዖታትን አትሥሩ አታምልኳቸውም፣ ምክንያቱም እኔ፣ ያህዌ ቀናተኛ አምላከ ነኝ። ስሜንም በከንቱ አትጥሩ፣ የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ ዐስብ። ይኸውም ሥራህን ሁሉ በስድስት ቀን ሥራ፣ ሰባተኛው ቀን ግን የምታርፍበትና እኔን የምታስታውስበት ዕለት ነው።››

Image

‹‹አባትህንና እናትህን አክብር። አትግደል። አታመንዝር። አትስረቅ። አትዋሽ። የባልንጀራህን ሚስት፣ ቤቱን፣ ወይም የእርሱ የሆነውን ማንኛውም ነገር አትመኝ።››

Image

ከዚያም እግዚአብሔር እነዚህን ዐሥር ትእዛዛት በሁለት ጠፍጣፋ ድንጋዮች ላይ ጽፎ ለሙሴ ሰጠው። ደግሞ እግዚአብሔር የሚከተሉአቸውን ሌሎች ብዙ ሕግጋትንና ደንቦችን ሰጣቸው። ሕዝቡ እነዚህን ሕግጋት ከታዘዙ እግዚአብሔር እንደሚባርካቸውና እንደሚጠብቃቸው ተስፋ ሰጣቸው። ሕግጋቱን ካልታዘዙ ግን እግዚአብሔር ይቀጣቸዋል።

Image

ደግሞም እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን እንዲሠሩለት ስለሚፈልገው ድንኳን ዝርዝር መግለጫ ሰጣቸው። እርሱ የመገናኛው ድንኳ ተብሎ ይጠራ ነበር፣ በትልቅ መጋረጃ የተከፈሉ ሁለት ክፍሎችም ነበሩት። እግዚአብሔር በዚያ ይኖር ስለ ነበረ፣ ከመጋረጃ በስተጀርባ ወዳለው ክፍል እንዲገባ የተፈቀደለት ሊቀ ካህን ብቻ ነበር።

Image

የእግዚአብሔርን ሕግ ያልታዘዘ ማንኛውም ሰው በመገናኛው ድንኳ ፊት ለፊት ወዳለው መሠዊያ ለእግዚአብሔር መሥዋዕት የሚሆን እንስሳ ያመጣ ነበር። ካህኑ እንስሳውን ያርድና በመሠዊያው ላይ ያቃጥለው ነበር። የተሠዋው እንስሳ ደም የሰውዬውን ኃጢአት ይሸፍንና ሰውዬውን በእግዚአብሔር ፊት ያነጻው ነበር። እግዚአብሔር ካህናቱ ይሆኑ ዘንድ የሙሴን ወንድም አሮንንና፣የአሮንን ዝርያዎች መረጠ።

Image

ሕዝቡ ሁላቸውም እግዚአብሔር የሰጣቸውን ትእዛዛት ለመፈጸም፣ እግዚአብሔርን ብቻ ለማምለክ፣ እንዲሁም የተለዩ ሕዝቡ ለመሆን ተስማሙ። ነገር ግን ለእግዚአብሔር ለመታዘዝ ቃል ከገቡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ክፉኛ ኃጢአት ሠሩ።

Image

ሙሴ ለብዙ ቀናት በሲና ተራራ ጫፍ ላይ ሆኖ ከእግዚአብሔር ጋር ይነጋገር ነበር። ሕዝቡ እርሱ እስኪመለስ ድረስ መጠበቅ ሰለቻቸው። ስለዚህ ወደ አሮን ወርቅ አመጡና ጣዖት እንዲሠራላቸው ጠየቁት!

Image

አሮንም በጥጃ ቅርፅ የወርቅ ጣዖት ሠራ። ሕዝቡም ልቅ በሆነ ሁኔታ ጣዖቱን ማምለክ ጀመሩ፣ መሥዋዕትም ሠዉለት! በኃጢአታቸው ምክንያት እግዚአብሔር በጣም ተቈጣቸው፣ ሊያጠፋቸውም ፈለገ። ነገር ግን ሙሴ ጸለየላቸው፣ እግዚአብሔርም ጸሎቱን ሰማና አላጠፋቸውም።

Image

ሙሴ ከተራራው ወርዶ ጣዖቱን ስያምልኩ ባየ ጊዜ በጣም ተቈጥቶ እግዚአብሔር ዐሥሩን ትእዛዛት የጻፈባቸውን ድንጋዮች ሰባበረ።

Image

ከዚያም ሙሴ ጣዖቱን ፈጨው፣ በውሃውም ላይ በተነው፣ ለሕዝቡም አጠጣቸው። እግዚአብሔር በሕዝቡ ላይ መቅሠፍት ላከና ብዙዎቻቸው ሞቱ።

Image

ሙሴ እንደ ገና ተራራው ላይ ወጣና እግዚአብሔር ሕዝቡን ይቅር እንዲላቸው ጸለየ። እግዚአብሔር ሙሴን ሰማውና ይቅር አላቸው። ሙሴ የሰባበራቸውን ለመተካት በዐዲስ ጠፍጣፋ ድንጋዮች ላይ የተጻፉትን ዐሥሩን ትእዛዛት ይዞ ከተራራ ወረደ። ከዚያ በኋላ እግዚአብሔር እስራኤላውያንን ከሲና ተራራ ወደ ተስፋዪቱ ምድር መራቸው።

የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ፡- ከዘጸአት 19-34፡፡